❖
ደብረ ታቦር ❖ [ ክፍል 3 ]
የጴጥሮስ ልመና ሊቀ ሐዋርያ ቅዱስ ጴጥሮስም በትሕትና ሁኖ አንዱን ላንተ፣ አንዱን ለሙሴ አንዱንም ለኤልያስ ሦስት ዳስ እንሥራና በዚህ እንኑር ብሎ ጠየቀ፤ ለእርሱና አብረውት ለነበሩት ወንድሞቹ ግን እንሥራ ባለማለቱ ትሕትናውን ገለጠ።
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ "የመብራት ፈትል ያለ ዘይት፤በጾምና ጸሎት መትጋትስ ያለ የዋህነት፣ ቤተክርስቲያንን መከተል ለድሆች ያለ መራራት፣ ድንግልናም ያለ ትሕትና ምን ይጠቅማል?" በማለት ገልጦታል። መ.ምሥጢር 30፥26
[
ኢየሱስ ክርስቶስ ከተራራው ወረደ]
/ማቴ 17፥9/
ለምኑ ይሰጣችኋል፣ ፈልጉ ታገኛላችሁ፣ አንኳኩ ይከፈትላችኋል ያለ አምላክ ቅዱስ ጴጥሮስ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው ብሎ እየለመነው እርሱ ግን ከተራራው ወረደ።
ለምንድነው የወረደው ስንል ከተራራው ካልወረደ የሰው ልጅ አይድንምና ነው።
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመጽሐፈ ምሥጢር የደብረ ታቦርን ምንባብ በጻፈበት ክፍል ላይ " ጴጥሮስ ሆይ ላንተ በታቦር ተራራ ላይ ድምጹን እየሰማሁ የሙሴ የኤልያስ ጌታ ይበሉህ እንጂ ሙሴ፣ ኤልያስ ልትባል አይገባህም የሚለውን ምሥክርነት እያደመጥክ በዚያ መኖር መልካም ነው። ለእኛ ግን ከተራራው ወርዶ በጥፊ ካልተመታልን ( ካልተሰቀለልን) አንድንምና በተራራው እንዲኖር አትለምነው።" በማለት ጌታ ከተራራው የወረደበትን ዓላማ በግልጥ አስቀምጦልናል።
[
ደብረ ታቦር የምን ምሳሌ ነው?]
ደብረ ታቦር ቤተክርስቲያን ናት ። ደብረ ታቦር ከፍ ያለ ተራራ እንደሆነ ሁሉ ቤተክርስቲያን በዚህ ዓለም ካሉ ቤቶች ሁሉ ክብሯ ከፍ ያለ ነውና " የመቅደሳችን ስፍራ ከጥንት ጀምሮ ክፍ ያለ የክብር ዙፋን ነው። "እንዲል /ኤር 17፥12/
እመቤታችን ደብረ ታቦር ትባላለች። ቅዱስ ያሬድ "ያቺ ተራራ የረጃጅሞች ተራሮች ራስ ቅድስት ድንግል ማርያም ናት፤ በማለት ቅዱስ ተራራ እመቤታችን መሆኗን ገልጧል።
ልበ አምላክ ዳዊትም "መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን" በማለት ክብራቸው ከከበሩ አበው እንደተወለደች ተራራ በማለት መስክሯል።
ደብረ ታቦር በወንጌል ትመሰላለች ። ተራራ ከፍ ያለ ነው ወንጌልም ከመጻሕፍተ ምኑናት፣ ከመጻሕፍ ርኵሳት፣ መጻሕፍተ ዕዳ ይልቅ የከበረች ናትና።
አንድም ተራራን ሲወጡት ያደክማል፣ ወንጌልን ሲፈጽሟት ያደክማል። ተራራ ከወጡት ኋላ ሁሉን እንዲያሳይ ወንጌልን ከተማሯት ኋላ ጽድቅን ከኃጢአት ለይታ ታሳያለችና ነው።
ደብረ ታቦር የመንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ነው። ተራራ ላይ በብዙ ጥረት እንደምንወጣ ሁሉ መንግሥተ ሰማያትም በብዙ መከራና ሕማም እንገባለንና ነው። /ሐዋ 14፥21/
ከዚህ ሁሉ የተነሣ ቅዱስ ጴጥሮስ ደብረ ታቦርን “ቅዱስ ተራራ” ብሎታል፡፡ /2 ጴጥ 1፥18/
ለሐዋርያት ብርሃነ መለኮቱን የገለጠ አምላክ የእኛንም ዓይነ ልቦናችንን ይብራልን!
- .....እንዴት #አደራችሁ ?
- .....እንዴት #አረፈዳችሁ ?
- .....እንዴት #ዋላችሁ ?
- .....እንዴት #አመሻችሁ ?
JOIN @Applied_CHRISTIANITY