ተግባራዊ ክርስትና


Гео и язык канала: Китай, Английский
Категория: Экономика


{ ከቅዱሳን ሕይወት ተማሩ ብለን እንለምናችኋለን }
"" ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ እንጂ ፤ ራሳችሁን እያሳታችሁ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ ! "" /ያዕ 1÷22/

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Китай, Английский
Категория
Экономика
Статистика
Фильтр публикаций




🔴 የአባታችን የዲያቢሎስ ምኞት !

"ብዙዎቻችን በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የዲያቢሎስን ምኞት እያሳካን ነው ።"

ሙሉ ትምህርት ተለቋል !

YouTube - https://youtu.be/h6HMqg87g_Y?si=Dxw7Y8f5rYUXAzNh


ልብ ብለህ አስተውል !

ያለፈውን በትምህርትነቱ ፣ ነገን በብልጫነቱ ፣ ዛሬን ግን በተጨባጭነቱ ውደደው ፡፡ ከትላንት ከመማር በቀር ወደ ኋላ መልሰህ ማደስ አትችልም ፡፡ ትላንት ላይ መዘግየት አመድ ላይ እንደ መንከባለል ነው ፡፡ መቆሸሽ እንጂ መንጻት የለውም ፡፡ ታሪክን ትማረዋለህ እንጂ አትቀየመውም ፡፡ ዛሬ ከትላንት የተሻለ እንደሆነ ነገም ከዛሬ የተሻለ ይሆናል ፡፡ ከትላንት ዛሬ እውቀትህ ጨምሯልና ዛሬ ከትላንት ትሻላለች ፡፡ ነገም ከዛሬ የተሻለ ታውቃለህና ብልጫ አላት ፡፡ ነገ እንደፈራኸው አይደለም ፣ ትላንት ላይ ዛሬ ነገ ነበረች ፡፡ እንደ ፈራሃት ግን አይደለችም ፡፡ ቀኑ ላይ ኃይል አለ ፡፡ እግዚአብሔር በቦታው አቅም ይሰጥሃል ፡፡ ራስህን እንደ ገመትከው አይደለህም ፡፡ በአስቸጋሪ ቦታዎች ላይ አቅም ይሰጥሃል ፡፡ በክፉ ቀኖች ቆራጥ ያደርግሃል ፡፡

የከሰርከውን ነገር በገንዘብ እንደ ተማርከው ትምህርት ቁጠረው ፡፡ ያገኘኸውን እንደምታጣው አድርገህ ያዘው ፡፡ የምትመኘውን በትዕግሥት ጠብቀው ፡፡ ወደፊት ምን ይመጣ ይሆን ብለህ አትጨነቅ ፡፡ የፈራኸው ቢመጣም ከዚህ በላይ አትታወክም ፡፡ ባልመጣ ቀን የመጣውን ቀን አትረብሸው ፣ የመጣውን ቀን ትተህም ባልመጣ ቀን አከናውናለሁ አትበል ፡፡ አንተ የአሁን ሰው ነህ ፡፡ ስትተኛ ለመንቃትህ ፣ ስትወጣ ለመመለስህ ምንም ዋስትና የለህም ፡፡ በማይረቡ ነገሮች አእምሮህን አታጣብ ፡፡ ችግሮችን ከምንጫቸው ትተህ ከወራጁ ከገደብህ ይደገማሉ ፡፡ እነዚያን ክፉ ቀኖች ካልረሳህ ዛሬን ይረብሻሉ ፡፡ ፍቅር የሰጡህን ሰዎች ካላመሰገንህ ነፍስህ በውለታ እስረኛ ትሆናለች ፡፡ ሞተህም የምትወቀሰው አደራ በማጥፋትህ ነውና ታማኝ ሁን ፡፡ የሞተ ሰው የገደለውን ያውቃል ፣ ነገር ግን ነቅቶ አይከስስም ፡፡ ትልቁ ዳኛ ጋር እየሄደ ነውና ፡፡ እግዚአብሔር ከተናገረልህ አንተ ዝም በል ፡፡ እግዚአብሔር ሲናገር አንተ ከተናገርህ ሁሉን ነገር ታበላሻለህ ፡፡

- .....እንዴት #አደራችሁ ?
- .....እንዴት #አረፈዳችሁ ?
- .....እንዴት #ዋላችሁ ?
- .....እንዴት #አመሻችሁ ?

JOIN @Applied_CHRISTIANITY

627 0 13 5 11

እንኳን ለእመቤታችን ትንሣኤ እና ዕርገት በሰላም አደረሳችሁ!

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጥር 21 ቀን በ64 ዓመቷ ከዚህ ዓለም ውጣ ውረድና ድካም ባረፈች ጊዜ ቅዱሳን ሐዋርያት ሊቀብሯት ወደ ጌቴሴማኒ ይዘዋት ሔዱ፡፡ በዚህ ጊዜ አይሁድ "እንደ ልጇ 'ተነሣች፤ ዐረገች' እያሉ እንዳያውኩን በእሳት እናቃጥላት" ብለው ሥጋዋን ሊያጠፉ በዓመፃ ተነሡ፡፡ ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊም አጎበሩን ይዞ ሊያወርዳት ሲል የእግዚአብሔር መልአክ ሁለት እጆቹን ቀጣው፡፡

ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር አምላክ ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስን ጨምሮ እመቤታችንን በደመና ነጥቆ ወደ ገነት ወስዶ ከዕፀ ሕይወት ሥር አስቀመጣት ቅዱሳን ሐዋርያትም እመቤታችን ያለችበት ቦታ እንዲገለጥላቸው ከነሐሴ 1 ቀን ጀምረው ሱባዔ ገብተው እግዚአብሔርን በጸሎት መጠየቅ ጀመሩ፡፡

ቅዱሳን ሐዋርያት ሁለት ሱባዔ (ዐሥራ አራት ቀናት) ካደረሱ በኋላም የነገሩትን የማይረሳ፣ የለመኑትን የማይነሳ እግዚአብሔር አምላካችን ጸሎታቸውን ሰምቶ የእመቤታችንን ሥጋ ሰጥቷቸው በክብር ገንዘው በጌቴሴማኒ ቀብረዋታል፡፡ በሦስተኛው ቀንም እንደ ልጇ እንደ ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይታ ተነሥታለች፡፡

ትንሣኤዋን "ከመ ትንሣኤ ወልዳ (እንደ ልጇ ትንሣኤ)" ያሰኘውም ይህ ምሥጢር ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ሲሰብክ ቆይቶ ደመና ጠቅሶ ከሀገረ ስብከቱ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመጣ እመቤታችን ከሙታን ተለይታ ተነሥታ ወደ ሰማይ ስታርግ ጠፈር ላይ አገኛት፡፡ በዚህ ጊዜ "ቀድሞ የልጅሽን ትንሣኤ፤ ዛሬ ደግሞ ያንቺን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁን?" ብሎ ትንሣኤዋን ባለማየቱ ኀዘን ስለ ተሰማው ከደመናው ይወድቅ ዘንድ ወደደ፡፡

እመቤታችንም "አይዞህ! አትዘን፤ ባልንጀሮችህ ሐዋርያት ያላዩትን ትንሣኤዬን አንተ አይተሃልና ደስ ይበልህ!" ብላ ከሙታን ተለይታ መነሣቷንና ማረጓን ለሐዋርያት እንዲነግራቸው  አዝዛ የያዘቸውን ሰበን ሰጥታ ሰደደችው፡፡ ከዚያም እርሷ ወደ ሰማይ ዐረገች፤ እርሱም ወደ ኢየሩሳሌም ወረደ፡፡

ቅዱስ ቶማስ ትእዛዟን ተቀብሎ በክብር ከተሰናበታት በኋላ ወደ ሐዋርያት ሔዶ እንዳልሰማ እንዳላየ መስሎ "የእመቤታችን ነገር እንደምን ሆነ?" ሲል ጠየቃቸው፡፡ እነርሱም "አግኝተን ቀበርናት" ሲሉት "ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር እንዴት ይኾናል?" አላቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስ ከዚህ በፊት የክርስቶስን ትንሣኤ መጠራጠሩን ጠቅሶ እየገሠፀ መከራከሩንና መጠራጠሩን ትቶ ስለ እመቤታችን መቀበር እነርሱ የሚነግሩትን ዅሉ አምኖ መቀበል እንደሚገባው ለቅዱስ ቶማስ አስረዳው፡፡

ቅዱስ ቶማስም የያዘውን ያውቃልና ጸጥ ብሎ ሲሰማው ቆየ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ተቈጥቶ የእመቤታችንን ክቡር ሥጋ ለቅዱስ ቶማስ ለማሳየት ሔዶ መቃብሯን ቢከፍት የእመቤታችንን ሥጋ ሊያገኘው አልቻለም፡፡ በዚህ ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስ ደንግጦ ቆመ፡፡

ቅዱስ ቶማስም "ወንድሞቼ! አታምኑኝም ብዬ ነው እንጂ እመቤታችንስ ከሙታን ተለይታ ተነሥታ ስታርግ አግኝቻታለሁ" ብሎ እመቤታችን የሰጠችውን ሰበን ለሐዋርያት ሰጥቷቸዋል፡፡ እነርሱም በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ትንሣኤና ዕርገት እየተደሰቱ ሰበኑን ለበረከት ተካፍለውታል፡፡

ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንደሚያስተምሩን በቅዳሴ ጊዜ ሠራዒ ዲያቆኑ በሚይዘው መስቀል ላይ የሚታሠረው መቀነት መሰል ልብስ፤ እንደዚሁም አባቶች ካህናት በመስቀላቸው ላይ የሚያደርጉት ቀጭን ልብስና በራሳቸው ላይ የሚጠመጥሙት ነጭ ሻሽ የእመቤታችን ሰበን ምሳሌ ነው፡፡

ከበዓሉ ረድኤት በረከት ያሳትፈን የእናታችን የእመቤታችን  የንጽህተ ንጹሐን ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም አማላጅነቷ አይለየን!!!


JOIN @Applied_CHRISTIANITY

816 0 13 2 17





ለወዳጅ ዘመድ እንዲሁም ክርስትያኖች በማጋራት ክርስቲያናዊ ትብብራችሁን እንድታሳዩን ስንል እንጠይቃለን ::
ክብረት ይስጥልን ::




ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ታቦር ብርሃነ መለኮቱን ፣ ክብረ መንግሥቱን ለገለጠበት በዓለ ደብረ ታቦር በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ ። መልካም በዓል !

"" እስመ ውእቱ ቀደመ አእምሮ ወዜነዎሙ ለአርዳኢሁ በደብረ ታቦር በእንተ መንግሥቱ ዳግመ ምጽአቱ በዐቢይ ስብሐት ። ""
#ትርጉም ፦ እርሱ አስቀድሞ አውቆ ለሐዋርያት በደብረ ታቦር ስለመንግሥቱ ፍጻሜና ዳግመኛ ስለመምጣቱ ነገራቸው ። /ቅዱስ ያሬድ/

JOIN @Applied_CHRISTIANITY


ደብረ ታቦር ❖ [ ክፍል 3 ]

የጴጥሮስ ልመና

ሊቀ ሐዋርያ ቅዱስ ጴጥሮስም በትሕትና  ሁኖ አንዱን ላንተ፣ አንዱን ለሙሴ አንዱንም ለኤልያስ ሦስት ዳስ እንሥራና በዚህ እንኑር ብሎ ጠየቀ፤ ለእርሱና አብረውት ለነበሩት ወንድሞቹ ግን እንሥራ ባለማለቱ ትሕትናውን ገለጠ።

አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ "የመብራት ፈትል ያለ ዘይት፤በጾምና ጸሎት መትጋትስ ያለ የዋህነት፣ ቤተክርስቲያንን መከተል ለድሆች ያለ መራራት፣ ድንግልናም ያለ ትሕትና ምን ይጠቅማል?" በማለት ገልጦታል። መ.ምሥጢር 30፥26 

[ ኢየሱስ ክርስቶስ ከተራራው ወረደ]
              /ማቴ 17፥9/

ለምኑ ይሰጣችኋል፣ ፈልጉ ታገኛላችሁ፣ አንኳኩ ይከፈትላችኋል ያለ አምላክ ቅዱስ ጴጥሮስ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው ብሎ እየለመነው እርሱ ግን ከተራራው ወረደ።

ለምንድነው የወረደው ስንል ከተራራው ካልወረደ የሰው ልጅ አይድንምና ነው።

አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመጽሐፈ ምሥጢር የደብረ ታቦርን ምንባብ በጻፈበት ክፍል ላይ " ጴጥሮስ ሆይ ላንተ በታቦር ተራራ ላይ ድምጹን እየሰማሁ የሙሴ የኤልያስ ጌታ ይበሉህ እንጂ ሙሴ፣ ኤልያስ ልትባል አይገባህም የሚለውን ምሥክርነት እያደመጥክ በዚያ መኖር መልካም ነው። ለእኛ ግን ከተራራው ወርዶ በጥፊ ካልተመታልን ( ካልተሰቀለልን) አንድንምና በተራራው እንዲኖር አትለምነው።" በማለት ጌታ ከተራራው የወረደበትን ዓላማ በግልጥ አስቀምጦልናል።

[ደብረ ታቦር የምን ምሳሌ ነው?]

ደብረ ታቦር ቤተክርስቲያን ናት ። ደብረ ታቦር ከፍ ያለ ተራራ እንደሆነ ሁሉ ቤተክርስቲያን በዚህ ዓለም ካሉ ቤቶች ሁሉ ክብሯ ከፍ ያለ ነውና " የመቅደሳችን ስፍራ ከጥንት ጀምሮ ክፍ ያለ የክብር ዙፋን ነው። "እንዲል /ኤር 17፥12/

እመቤታችን ደብረ ታቦር ትባላለች። ቅዱስ ያሬድ  "ያቺ ተራራ የረጃጅሞች ተራሮች ራስ  ቅድስት ድንግል ማርያም ናት፤ በማለት ቅዱስ ተራራ እመቤታችን መሆኗን ገልጧል።

ልበ አምላክ ዳዊትም "መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን" በማለት ክብራቸው ከከበሩ አበው እንደተወለደች ተራራ በማለት መስክሯል።

ደብረ ታቦር በወንጌል ትመሰላለች ። ተራራ ከፍ ያለ ነው ወንጌልም ከመጻሕፍተ ምኑናት፣ ከመጻሕፍ ርኵሳት፣ መጻሕፍተ ዕዳ ይልቅ የከበረች ናትና።

አንድም ተራራን ሲወጡት ያደክማል፣ ወንጌልን ሲፈጽሟት  ያደክማል። ተራራ ከወጡት ኋላ ሁሉን እንዲያሳይ ወንጌልን ከተማሯት ኋላ ጽድቅን ከኃጢአት ለይታ ታሳያለችና ነው።

ደብረ ታቦር የመንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ነው። ተራራ ላይ በብዙ ጥረት እንደምንወጣ ሁሉ መንግሥተ ሰማያትም በብዙ መከራና ሕማም እንገባለንና ነው። /ሐዋ 14፥21/

ከዚህ ሁሉ የተነሣ ቅዱስ ጴጥሮስ ደብረ ታቦርን “ቅዱስ ተራራ” ብሎታል፡፡ /2 ጴጥ 1፥18/

ለሐዋርያት ብርሃነ መለኮቱን የገለጠ አምላክ የእኛንም ዓይነ ልቦናችንን ይብራልን!


- .....እንዴት #አደራችሁ ?
- .....እንዴት #አረፈዳችሁ ?
- .....እንዴት #ዋላችሁ ?
- .....እንዴት #አመሻችሁ ?

JOIN @Applied_CHRISTIANITY


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
መጣሁኝ ከደጅሽ ፍቅርሽ ይጠራኛል
ስዕልሽ ስር ቆሜ ዕንባዬ ይቀድመኛል


🔴 ሙሉ መዝሙር ተለቋል - https://youtu.be/vq4VwYlmz2I?si=KTn4I23Re0Imq0-X




ደብረ ታቦር ❖  [ ክፍል 2 ]

ብርሃነ መለኮቱን ለምን ገለጠ?

1.ነሐሴ ሰባት ቀን በቂሳርያ ደቀ መዛሙርቱን “ሰዎች የሰውን ልጅ ማን ይሉታል?” ብሎ በጠየቃቸው ጊዜ ኤርምያስ ነው፣ ኤልያስ ነው፣ ዮሐንስ መጥምቅ ነው፣ ከነቢያት አንዱ ነው፣ ይሉሀል የሚል የተለያየ መልስ ተሰጥቶት  “እናንተስ ማን ትሉኛላችሁ?” ባላቸው ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስ “አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ” ብሎ መስክሯል ፡፡ ስለሆነም በፍጡር ቃል የተመሰከረውን በባሕርይ አባቱ ለማስመስከር

2.ከነቢያት አንዱ ነው ብለውት ነበርና እግዚአ ነቢያት (የነቢያት ጌታ) እንደሆነ ለማስረዳት

3.እሞታለሁ እሰቀላለሁ ሲል ጴጥሮስ “ሀሰ ለከ” ልትሞት አይገባህም ብሎት ነበርና እርሱን ስሙት ለማለት ።

ወንጌላውያን መግለጥ በሚችሉት መጠን ከገለጹት ያለፈ ልናብራራው የምንችለው አይደለም ፡፡ ማቴዎስ እንዲህ ይገልጸዋል “በፊታቸውም ተለወጠ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ” /ማቴ 17፥2/ ብሎ ወንጌላዊው በዚህ ዓይነት ገለጾ የተናገረው ምሳሌ ስለ አጣለት ነው ፡፡

ማርቆስም ይህንኑ ተጋርቶ “ልብሱን አንፀባረቀ አጣቢም በምድር ላይ እንደዚያ ሊያነጣው እስከማይችል በጣም ነጭ ሆነ” /ማር 9፥2-4/

የፊቱ መልክ ተለወጠ ልብሱም ተብለጭልጮ ነጭ ሆነ” /ሉቃ 9፥29-30/

በደብረ ታቦር ሐዋርያት ካዩት በተጨማሪ አብ በደመና ሆኖ የምወደው ልጄ ነው እርሱን ስሙት ሲል ተሰምቷል ። መንፈስ ቅዱስም በአምሳለ ርግብ ታይቶ አንድነት ሦስትነት ተገልጿል ፡፡

  [ልብሱ እንደ በረዶ ነጭ ሆነ]

የልብሱን ጸአዳነት ሊቁ ርቱዓ ሃይማኖት (አባ ጊዮርጊስ) "መጀመሪያ በአዳም የነበረው የብርሃን ልብስ ዛሬ ተመለስ ፡፡ ያረጀ የአዳም ሰውነት ዛሬ ታደሰ፤ መጀመሪያውና ኋለኛው ዛሬ በደብረ ታቦር ታደስ ፡፡ ፊቱም እንደ ፀሐይ አበራ፤ ዛሬ ክርስቶስ በፍጥረቱ ሁሉ ተሾመ ፡፡ ዛሬ ንግሥናው ከዓለም አስቀድሞ የነበረ የነገሥታቱ ንጉሥ የሹመቱ ዕለት ነው ፡፡ ዛሬ ነጭ ልብሱ እንደ በረዶ ነጭ ሆነ ፡፡ በምድር ያለ አጣቢም እንዲህ ሊያነጻው አይችልም ፡፡ ባለሳሙናዎቹም በትክክል አጥበው የሚያነጹት አይደለም ፡፡ ይህ የንግሥና ልብስም በውኃ የሚያጥቡት አይደለም ፡፡ በወይን ደም ነው እንጂ ፡፡ " በማለት አመሥጥሮታል ።

- .....እንዴት #አደራችሁ ?
- .....እንዴት #አረፈዳችሁ ?
- .....እንዴት #ዋላችሁ ?
- .....እንዴት #አመሻችሁ ?

JOIN @Applied_CHRISTIANITY




ደብረ ታቦር ❖  [ ክፍል 1 ]

ደብር ተራራ ሲሆን፣ ታቦር ደግሞ የተራራው ስም ነው። የበዓሉ ስያሜ የተወሰደው ነቢዩ ዳዊት “ታቦርና አርሞንኤም በስምህ ደስ ይላቸዋል” በማለት ከተናገረው የትንቢት ቃል ነው ። /መዝ 88፥12/

ደብረ ታቦር በቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከዘጠኙ ዐበይት በዓላት የሚመደብ ነው ።  ከዐበይት በዓላት የተመደበበትም ምክንያት በደብረ ታቦር የተገለጸው ምሥጢር ድንቅ መሆኑ ነው ።

ጌታችን ለሐዋርያት በተለያየ ቦታ ምሥጢር የገለጠላቸው ሲሆን ደብረ ታቦርን ከሌሎቹ ልዩ የሚያደርገው ከሐዋርያት ጴጥሮስ፣ ዮሐንስና ያዕቆብ ያሉ ሲሆን ከነቢያት ሙሴና ኤልያስ መጨመራቸው ነው ።

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሁሉም ምሥጢራት ነገረ ምጽአቱንና ምሥጢረ መንግሥቱን በተራራ ላይ ገልጿል፡፡ ነገረ ምጽአትን በደብረ ዘይት፣ ምስጢረ መንግስቱን በደብረ ታቦር ገልጿል ።

👉ደብረ ታቦር ለምን ተመረጠ?

[የድል ተራራ ስለሆነ]

የእስራኤል ነቢይት ዲቦራ ለባርቅ የእስራኤል ጠላት የነበረው የኢያቢስን የሠራዊት አለቃ ሲሣራን ለመውጋት ወደ ደብረ ታቦር አስር ሺ ሰዎችን አስከትሎ እንዲወጣ ነግራዋለች ። /መሳ 4፥6/

ሲሣራ ዘጠኝ መቶ የብረት ሠረገላ እንዲሁ ብዙ ሠራዊትም በታቦር ያሰለፈ ቢሆንም ድል ግን ረድኤተ እግዚብሔርን ጥግ ላደረገ ለባርቅ ሆነ ። በዚህ ጊዜ ዲቦራ በታቦር ተራራ የሙሴ እኅት ማርያም በኤርትራ ባሕር የዘመረችውን መዝሙር የመሠለ ምስጋና አቅርባለች ፡፡

ጌታችንም የባሕርይ አምላክነቱን ገልጾ ከደቀ መዛሙርቱ ልቡና አጋንንትን የሚያባርርበት ዲያብሎስን ድል የሚነሳበት ስለሆነ ከሌሎች ተራሮች ተመርጧል፡፡

[ትንቢት ስለተነገረለት]

ታቦር ወአርሞንዔም በስመ ዚአከ ይትፌስሑ ወይሴብሑ ለስምከ ። /መዝ 88፥12/ ብሎ ቅዱስ ዳዊት አምላካችን ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን በደብረ ታቦር እንደሚገልጽ ብርሃኑ ከደብረ ታቦር እስከ አርሞንዔም ድረስ እንደሚታይ ይህም መለኮታዊ ብርሃን በታቦርና በአርሞንዔም ዙሪያ ለነበሩ ሕዝቦች ደስታ እንደሚሆን ተናግሯል፡፡

ስለዚህ ተራራ ቅዱስ ዳዊት በድጋሜ እንዲህ በማለት ትንቢት ተናግሮለታል፦

የእግዚአብሔር ተራራ የለመለመ ተራራ ነው ። የጸና ተራራ የለመለመ ተራራ ነው ። እግዚአብሔር ይህን ተራራ ያድርበት ዘንድ ወደደው” /መዝ 67፥15/ ብሎ እግዚብሔር ብርሃነ መለኮቱን እንደሚገልጥበት ዘምሮአል፡፡

#ይቀጥላል...
   
- .....እንዴት #አደራችሁ ?
- .....እንዴት #አረፈዳችሁ ?
- .....እንዴት #ዋላችሁ ?
- .....እንዴት #አመሻችሁ ?

JOIN @Applied_CHRISTIANITY




"ዲያብሎስ በእናንተ ላይ እጅግ ክፉ ነገርን በማምጣት አሳዝኖአችኋልን? እናንተም ኢዮብን አብነት አድርጋችሁ እግዚአብሔር ይመስገን በማለት አሳዝኑት፡፡ ዲያብሎስን ድል ማድረግ ስትሹ ይህን መሣርያ ዘወትር ያዙ፤ ምስጋናን፡፡"

( ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ )

JOIN @Applied_CHRISTIANITY




Репост из: SSC ቅድመ ግቢ ጉባኤ
አቤል ይባላል የግቢ ጉባኤያችን አባልና የ12ኛ ክፍል ተማሪ ነው። አሁን ግን እንደምትመለከቱት አደጋ አጋጥሞት የእኛን እርዳታ ይፈልጋልና የምንችለውን ያህል ከላይ በተጠቀሱት አካውንቶች በመላክ እናግዘው።

ማጋራትም እርዳታ ነውና ይህን ፖስት ለምናውቃቸው ሰዎች በማድረስ እነርሱም እንዲያግዙ እናድርግ።
CBE: 1000348860538
Telebirr: 0911398024 / 0931534451


በእንተ ሱባኤ !

ሱባኤ በሰዋስው ትርጉሙ ሰባት ማለት ነው ፡፡ ሰባት ቁጥር በእስራኤላውያን ዘንድ በሥራም በቃልም የሚገለጥ ፍጹም ቁጥር ነው ፡፡ እግዚአብሔር በሰባተኛው ቀን ሥነ ፍጥረት ፈጥሮ አጠናቋል ፡፡ ‹‹እግዚአብሔርም የሠራውን ሥራ በሰባተኛው ቀን ፈጸመ›› እንዲል /ዘፍ.2፥2/ ፡፡ ቅዱስ ዳዊትም ‹‹ስለ ጽድቅህ ፍርድ ሰባት ጊዜ በቀን አመሰግንሃለሁ›› በማለት ለጸሎት የሚተጉ ምእመናን በቀን ለሰባት ጊዜ እግዚአብሔርን ማመስገናቸው እንዳለባቸው ይመክራል /መዝ.118፥164/ ፡፡ ሱባኤ በመንፈሳዊ ትርጉሙም አንድ ሰው ከዚህ ቀን እስከዚህ ቀን በጸሎት ከፈጣሪዬ እገናኛለሁ ብሎ የሚያቅደው መንፈሳዊ እቅድ ነው ፡፡ ከዚህ አንጻር አንድ ሰው ለሰባት ቀናት ቢጾም «አንድ ሱባኤ ጾመ» ለዐሥራ አራት ቀን ቢጾም «ሁለት ሱባኤ ጾመ» ይባላል ፡፡

ሱባኤ የተጀመረው ከውድቀት በኋላ በመጀመሪያው ሰው በአዳም ነው ፡፡ አዳም በገነት ሰባት ዓመት ከአንድ ወር ከዐሥራ ሰባት ቀን በደስታ ከኖረ በኋላ ሕግ አፍርሶ የፈጣሪውን ቃል ጥሶ ከገነት ወጥቷል ፡፡ መልሶ ፈጣሪው እንዲታረቀው ሠላሣ አምስት ቀን ሱባኤ ገብቷል ፡፡ በመጨረሻም ‹‹በሐሙስ ዕለት ወበመንፈቃ ለዕለት እትወለድ እምወለተ ወለትከ ወእደኅከ ውሰተ መርሀብከ›› ብሎ ተስፋውን ሰጠው ፡፡ ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ አዳም ጥፋቱን አምኖ ከባሕር ውስጥ ሱባኤ በመግባቱና በመጸለዩ እግዚአብሔር በማይታበል ቃሉ «ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንኀለሁ» ሲል ቃል ኪዳን ገብቶለታል ፡፡

እንሆ የ2018 ዓ.ም ጾመ ፍልሰታ ነገ (ዕለተ አርብ ነሐሴ 1 ቀን) ይጀምራል ። የቻልን ጠዋት በኪዳን ከሰዓት በውዳሴ ማርያም ትርጓሜ እና በቅዳሴ ተገኝተን እናስቀድስ ። በሥራና በትምህርት ያልቻልን ደግሞ ሌሊት ኪዳን በማድረስ እናሳልፍ እላለሁኝ ።

መልካም ሱባኤ 🕊


JOIN @Applied_CHRISTIANITY

Показано 20 последних публикаций.